Saturday, August 25, 2012

አንግርጉሮ ነገር


አንግርጉሮ ነገር

ሰማን ከዛ ማዶ ከፋ አሉ ጫጫታው  
ባልታስብ ነገር ገዳይን ሞት ነካዉ 
ጀግና ነበር አሉ  ሎቴው ያማረለት 
ገዳይ ነበር አሉ አልሞ የማይስት 
አንዴት ያለ ነገር በሱ ደረሰበት 
ድንገተኛ  ሆኖ ካልሰማ ሀገሩ 
የሰሙትን  ጥሩ ካልሰሙም ንገሩ
የዛን  ገዳይ ጀግና አስከሬን ይቅበሩ 



Wednesday, March 17, 2010

የበረዶ ቤት

ጉልብት እንደሌለው
እራሱ እያወቀው
የሱ ለርሱ ብቻ ወቅቱ ስለሆነ
በነነ ገነነ
ላይሆን ደርቆ ቀልጦ የሚጠበስ እሸት
ታፍሶ ተጨልፎ ወጥ ላይሰራበት
ተቆፍሮ ታርሶ ሩዝ ላይበቅልበት
እያብለጨለጨ ወራት አለፈበት
እኛም አወቅንና የበረዶን ጉልበት
ዘዴ ዘየድንበት
ተንሸራተትንበት ተንከባለልበት
ጨብጠን በትነን ተደባድብንበት
ውዱም ውዳን ይዞ
እንጨት ተመርኩዞ
ብረት ተመርኮዞ
ጀመሩበት ጉዞ
ባይሞቅም ባይደላም
ነገሩ አያስጠላም
ውዲት ከውዱ ጋር ተነጋገሩና ምክር አመጡበት
በረዶን ሊሞቁት ጎጆ ቀለሱበት።

Monday, March 15, 2010

ወፍና ጠጠር

ቀኑ መሽቶ ነግቶ
ሌሊቱ በትግል ወጦ ተጎትቶ
ጧት ማለዳ ላይ
ዝማሬን አውጥቼ ሆኜ ጎጄ ላይ
የሚበላ ነገር አምሮኝ ስንዴ ነገር
ወረድኩ ባገኝ ብየ ተቀላቅሎ ካፈር
የዚህ ሀገር ነገር
ጠፍቶ ይሁን አፈር
ወይም ተደብቆ
በኖ በኖ ተበትኖ ደቆ
ወይ እግር በዝቶበት ሆኖ ይሁን ኮረት
አላውቅም እንጃለት
ብቻ እራበኝና አንጀቴ ብሶበት
ስንዴ መስሎኝ ለኔ ጠጠሩን በላሁት
ኮረቱን ለቀምኩት

Thursday, March 11, 2010

ቀን

ቀን ያልፋል

እስኪያልፍም ያለፋል

ባያልፍም ይገፋል

ይገፋል

ብሎም ያሳልፋል