Sama
Saturday, August 25, 2012
አንግርጉሮ ነገር
አንግርጉሮ ነገር
ሰማን ከዛ ማዶ ከፋ አሉ ጫጫታው
ባልታስብ ነገር ገዳይን ሞት ነካዉ
ጀግና ነበር አሉ ሎቴው ያማረለት
ገዳይ ነበር አሉ አልሞ የማይስት
አንዴት ያለ ነገር በሱ ደረሰበት
ድንገተኛ ሆኖ ካልሰማ ሀገሩ
የሰሙትን ጥሩ ካልሰሙም ንገሩ
የዛን ገዳይ ጀግና አስከሬን ይቅበሩ
Wednesday, March 17, 2010
የበረዶ ቤት
ጉልብት እንደሌለው
እራሱ እያወቀው
የሱ ለርሱ ብቻ ወቅቱ ስለሆነ
በነነ ገነነ
ላይሆን ደርቆ ቀልጦ የሚጠበስ እሸት
ታፍሶ ተጨልፎ ወጥ ላይሰራበት
ተቆፍሮ ታርሶ ሩዝ ላይበቅልበት
እያብለጨለጨ ወራት አለፈበት
እኛም አወቅንና የበረዶን ጉልበት
ዘዴ ዘየድንበት
ተንሸራተትንበት ተንከባለልበት
ጨብጠን በትነን ተደባድብንበት
ውዱም ውዳን ይዞ
እንጨት ተመርኩዞ
ብረት ተመርኮዞ
ጀመሩበት ጉዞ
ባይሞቅም ባይደላም
ነገሩ አያስጠላም
ውዲት ከውዱ ጋር ተነጋገሩና ምክር አመጡበት
በረዶን ሊሞቁት ጎጆ ቀለሱበት።
Monday, March 15, 2010
ወፍና ጠጠር
ቀኑ መሽቶ ነግቶ
ሌሊቱ በትግል ወጦ ተጎትቶ
ጧት ማለዳ ላይ
ዝማሬን አውጥቼ ሆኜ ጎጄ ላይ
የሚበላ ነገር አምሮኝ ስንዴ ነገር
ወረድኩ ባገኝ ብየ ተቀላቅሎ ካፈር
የዚህ ሀገር ነገር
ጠፍቶ ይሁን አፈር
ወይም ተደብቆ
በኖ በኖ ተበትኖ ደቆ
ወይ እግር በዝቶበት ሆኖ ይሁን ኮረት
አላውቅም እንጃለት
ብቻ እራበኝና አንጀቴ ብሶበት
ስንዴ መስሎኝ ለኔ ጠጠሩን በላሁት
ኮረቱን ለቀምኩት
Thursday, March 11, 2010
ቀን
ቀን ያልፋል
እስኪያልፍም ያለፋል
ባያልፍም ይገፋል
ይገፋል
ብሎም ያሳልፋል
።
Home
Subscribe to:
Posts (Atom)